(ሚያዝያ 8/2017 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የትምህርት ግብዓት ፍላጎት አቅርቦትና ስርጭት ዳይሬክቶሬት የ9ወር እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ግምገማ አካሂዷል::
የትምህርት ግብዓት ፍላጎት አቅርቦትና ስርጭት ዳይሬክተር ወ/ሮ ምስራቅ ብርሀነመስቀል የ9 ወር እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ባቀረቡበት ወቅት እንዳሉት በዘጠኝ ወራት ከቁልፍና አበይት ተግባራት አንፃር በርካታ ሥራዎች መከናወናቸውን ገልፀዋል ፤ በመንግስት ቅድመ አንደኛ አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የመማሪያ ቁሳቁስ ፣ የደንብ ልብስና የመማሪያ መፅሐፍ ስርጭትን ጨምሮ የምገባ ስርዓትን ተግባራዊነት በክትትልና ድጋፍ በመታገዝ በርካታ ሥራዎች መሰራታቸውን ያብራሩት ዳይሬክተሯ በቀሪ ወራት ሥራዎችን ከግብ ለማድረስ የቀደሙ ሥራዎችን መገምገም አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመዋል:: አያይዘውም የቀሪ ወራት የስራ አቅጣጫም አስቀምጠዋል ::
በተያያዘም ከስርአተ ትምህርት ለውጥ በኃላ የተከናወኑ የመፅሐፍ ህትመትና ስርጭት ሪፖርት የግብዓት አቅርቦት ከፍተኛ ባለሙያ በሆኑት በአቶ አሸናፊ ደጀኔ ቀርቦ በቀረቡት ሪፖርቶች ላይ ውይይት ተደርጎበታል::
በውይይቱ የስራ ክፍሉ ባለሞያዎችና የቢሮው የሁለቱ ስርዓተ ትምህርት ሱፐርቫይዘሮች እንዲሁም የክፍለ ከተማ የትምህርት ቤት መሻሻል ፣ የልዩ ፍላጎትና ዘርፈ ብዙ ቡድን መሪዎችና የግብዓት ባለሙያዎች ተሳትፈዋል::
.